torsdag 1. mai 2014

ጆን ኬሪ በአዲስ አበባ

ትናንት ማምሻዉን አዲስ አበባ የገቡት የአሜሪካን የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ ኢትዮጵያ ለሲቪክ ማኅበራትና ለጋዜጠኞች የተሻለ ነፃነት እንድትሰጥ ጠየቁ። ባለፈዉ ሳምንት ማለቂያ የታሠሩት የድረገፅ ጸሀፍትና ጋዜጠኞች ጉዳይም እንዳሳሰባቸዉ ገለጹ።
Kerry bei Treffen der Afrikanischen Union
ባለፈዉ ሳምንት ማለቂያ የታሠሩት የድረገፅ ጸሀፍትና ጋዜጠኞች ጉዳይም እንዳሳሰባቸዉ ገለጹ። ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ጋ ከተነጋገሩ በኋላ ኬሪ፤ ኢትዮጵያ ዉስጥም ሆነ የትም ቦታ የሚታሠሩ ጋዜጠኞች ጉዳይ እንደሚያሳስባቸዉ መግለፃቸዉን ማመልከታቸዉን የፈረንሳይ የዜና ወኪል ከአዲስ አበባ ዘግቧል። ጋዜጠኞች በህትመት፤ በኢንርኔትም ሆነ በትኛዉም ዓይነት መገናኛ ብዙሃን የሚያከናዉኑት ኅብረተሰቡን እንደሚያጠናክር፤ እንደሚያነቃቃና ፤ለዴሞክራሲም መጠናከርና ድምፅ ሊሆን እንደሚችልም ገልጸዋል። የመብት ተሟጋቾች በዓለማችን እጅግ የተዘጋ የፕረስ ሁኔታ ያላት ሀገር ኢትዮጵያ ናት በማለት ይተቻሉ። ጆን ኬሪ በሰጡት መግለጫ የጸረ ሽብር ሕግን ሃሳብን በነፃነት የመግለጽ መብትን ለማገጃ ሊናዉል አይገባም ማለታቸዉን ዘገባዉ ጨምሮ ጠቅሷል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar