mandag 5. mai 2014

73 ተኛው የድል በዓል

የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ አርበኞችና ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት በተካሄደው የበዓሉ አከባበር ስነ ስርዓት ላይ ለሃገራቸው የተዋደቁ አርበኞች የሚያገኙት የጡረታ ገንዘብ እንዲሻሻል ተጠይቋል ።
73. Jahrestag äthiopische Patrioten
ኢትዮጵያ በፋሺሽት ኢጣልያ ላይ ድል የተቀዳጀችበት 73 ተኛ ዓመት በዓል በመላው ኢትዮጵያ ዛሬ ተከብሮ ዋለ ። በዓሉ በተለይም በአዲስ አበባ በተለምዶ አራት ኪሎ ተብሎ በሚጠራው የድል አደባባባይ በሚገኝበት ስፍራ በድምቀት ተከብሯል ። የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ አርበኞችና ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት በተካሄደው የበዓሉ አከባበር ስነ ስርዓት ላይ ለሃገራቸው የተዋደቁ አርበኞች የሚያገኙት የጡረታ ገንዘብ እንዲሻሻል ተጠይቋል ።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar