fredag 24. oktober 2014

በትግራይ የሚገኘው ተጠባባቂ ጦር ለሕወሓት ጥሪ እንዲዘጋጅ ተነገረ


የደርግ የመጨረሻ “መሳሪያ ታጠቁልኝ “አመታቶች በወያኔም እየተደገሙ ነው።
– የደህንነት ሹሙ ባንክ ኦፍ አቡደሃቢ ያላቸውን 34 ሚሊዮን ዶላር ውስጥ 20 ሚሊዮኑን ወደ ማሌዢያ ባንኮች ማዘዋወራቸው ታወቀ።
በመሃል ሃገር ያለውን ጦር ሰሜን ግንባር ላይ አስፍሮ በምትኩ በትግራይ ክልል የሚገኘውን ትግሪኛ ተናጋሪ ተጠባባቂ ጦር በማስታጠቅ በመሃል አገር ላይ ለማስፈር እቅድ መያዙን በመከላከያ ሚኒስቴር የምድር ጦር መምሪያ ውስጥ የሚገኙ ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ ባደረሱት መረጃ ገልጸዋል።
ስርአቱ በመበስበስ ላይ መሆኑ እና ውድቀቱ መፋጠኑን በማወቁ ለሌላው ኢትዮጵያዊ ያለውን አመኔታ ስላጣ ለህዝብ ታማኝ አለመሆኑን ስላወቀው በዙሪያው የአንድ ብሄር ታጣቂ ጦር በመሰብሰብ እና ራሱን ከተከላካይነት ወደ አጥቂነት ለማሸጋገር እንዲሁም የትግራይ ተወላጅ ያልሆኑ ዜጎችን አንድ ችግር ቢከሰት መሃል ሃገሩን በማመስ በጅምላ ለመፍጀት እንዲያመቸው ይህንን ዘዴ በሕወሓት የተቀየሰ መሆኑ ታውቋል። በሃገሪቱ የሚገኙ የትግራይ ተወላጆችን በሙሉ በድጋሚ ለማስታጠቅ እና በተጠንቀቅ በሌላው ኢትዮጵያዊ ላይ ፍጅት ለመፍጠር ማቀዱን የተናገሩት ምንጮቹ እንደማይሳካለት እና የትግራይ ተወላጆችም እንደነቁ ገልጸዋል።
ደርግ በበሰበሰበት የመጨረሻው አመታቶቹ ካድሬዎቹን እና አጨብጫቢዎቹን ማስታጠቁ ከውድቀት አላዳነውም ያሉት ምንጮቹ አሁንም ሕወሓት የደርግን ባህርያት እየደገመ መሆኑን በገሃድ እየታየ ነው ብለዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የደህንነት ሹሙ የሆነው ጌታቸው አሰፋ ባንክ ኦፍ አቡደሃቢ በተሰኘ የአረብ ባንክ ውስጥ በዱባይ ድብቅ ውሽማው በሆነችው እና ከአቶ መላኩ ከተነጠቀችው በወይዘሮ ጸጋማርያም ገብረስላሴ ስም ተመዝግቦ ከሚገኘው 34 ሚሊዮን ዶላር ውስጥ 20 ሚሊዮኑን ወደ ማሌዢያ ባንክ ማዘዋወሩ ታውቋል። ወይዘሮዋ ጠቅልላ ሃገር ቤት ለመኖር ማቀዷን ተከትሎ በዱባይ የሚገኘውን ንብረቱን እና ገንዘቡን በመሰብሰብ ላይ እንደሚገኝ ታውቋል። እንዲሁም አቶ ኢሳያስ ወልደጊዮርጊስ የሚዘርፈውን ገንዘብ የሚልከው እና የሚያስቀምተው ካናዳ በምትገኘው እና እህቱ በሆነችው በቀድሞ የኪቤአድ ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ አወጣሽኝ ስም መሆኑ ይታወቃል ሲሉ ባለመረጃዎቹ ጨምረው ገልጸዋል።
ምንጭ፡ ምንሊክ ሳልሳዊ

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar