fredag 31. oktober 2014

የቡርኪናፋሶ ወጣቶች ተቃውሞ ባነሱ ማግስት መሪያቸውን አባረሩ




ለ27 አመታት አገሪቱን የመሩት ብሌስ ካምፓወሬ፣ እንደገና ለመመረጥ የነበራቸውን ፍላጎት ተቃውሞ መነሳቱን ተከትሎ መተዋቸውን ካስታወቁ በሁዋላ፣ የሽግግር መንግስት ፕሬዚዳንት በመሆን ለማገልገል መፈለጋቸውን ገልጸው ነበር። ይሁን እንጅ ተቃዋሚዎች ፕሬዚዳንቱ ከስልጣን ካልተባረሩ ተቃውሞአችንን አንተውም በማለታቸው፣ ፕሬዚዳንቱ ስልጣናቸውን መልቀቃቸውን አስታውቀዋል።
ተቃውሞቸውን ሲያሰሙ የነበሩት ሁሉ የመሪውን መውረድ እንደሰሙ ደስታቸውን ገልጸዋል። የአገሪቱ ጦር የሽግግር መንግስት እንደሚያቋቁሙ ገልጸው፣ የፕሬዚዳንቱን ቦታ በጊዜያዊነት መያዛቸውን አስታውቀዋል። ፈረንሳይ የፕሬዚዳንቱን ስልጣን መልቀቅ በደስታ ተቀብላዋለች። ቡርኪናፋሶ ከአረብ አብዮት በሁዋላ አምባገነን መሪን በተቃውሞ በማባረር ከሰሃራ በታች ካሉ አገራት የመጀመሪያዋ ሆናለች።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar