mandag 18. februar 2013

በዳውሮ ዞን የሚታሰሩ ሰዎች ቁጥር ጨምሯል



የመረጃ ምንጮች እንደገለጡት የእና አቶ ዱባል ገበየሁን እስር ተከትሎ የዩኒቨርስቲ መምህራን እና የመንግስት ሰራተኖች እየታሰሩ ነው።

ከአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ አቶ አባተ ኡካ፣ ከጅማ ዩኒቨርስቲ አቶ አብረሀም ሰሞኑን ተይዘው ታስረዋል።

በክልሉ የሚታየው ውጥረት መንግስትን በእጅጉ እንዳሳሰበው ለማወቅ ተችሎአል።

 የአቶ ዱባለ ገበየሁ ዘመዶችና ወዳጆችም እየተለቀሙ በመታሰር ላይ ሲሆኑ፣ ከግንቦት 7 ጋር በተያያዘ በአሸባሪነት ክስ እንደሚቀርብባቸው የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

ዳውሮ መምህር የኔሰው ገብሬ ዲሞክራሲና ፍትህ በሌለበት አገር አልኖርም በማለት ራሱን በእሳት አቃጥሎ ያገደለባት ቦታ ነው።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar