onsdag 20. februar 2013

በሰሜን ጎንደር የተለያዩ ፖለቲካዊና ማኀበራዊ ይዘት ያላቸው መፅሔቶችና መፅሐፎች እንዳይሸጡ ታገደ



ፍኖተ ነጻነት እንደዘገበው መጽሄቶችንና መፅሀፎችን አዙረው የሚሸጡ ወጣቶችም ከየካቲት 2 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮ የያዙዋቸው መጽሀፎችና መጽሄቶች ተወርሶባቸዋል።

በተለይ በጎንደር ከተማ ቀበሌ 11 ልዩ ስሙ አባጃሌ በሚባል አካባቢ ያሉ የደንብ አስከባሪዎች እዚህ ጎንደር ውስጥ ምንም ዓይነት ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸውን መፅሔቶች፣ ጋዜጦችና መፅሐፎች መሸጥ አትችሉም በሚል በተደጋጋሚ ጊዜ ከአዙሪዎች እየወረሱ ቅጣት እያሉ ያስከፍሏቸው እንደነበር ቢታወቅም የካቲት 2 ቀን 2005 ዓ.ም. ግን ሙሉ በሙሉ እንደወረሱባቸው ተዘግቧል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar