søndag 24. februar 2013

ካኤልም- ኤር ፍራንስ ወደ ኢትዮጵያ የሚያደርገውን በረራ ሰረዘ


የኔዘርላንድስ አየር መንገድ ወደ ኢትዮጵያ የሚያደርገውን በረራ የሰረዘው አትራፊ ባለመሆኑ ነው ብሎአል።

ድርጅቱ ለሪፖርተር እንደገለጠው ወደ ኢትዮጵያ የሚያደርገውን በረራ ከተለያዩ አየር መንገዶች በገጠመው ውድድር እንዲሁም የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ በማሳየቱ ለመሰረዝ ተገዷል።

“ወደ ኢትዮጵያ የምናደርገው በረራ አትራፊ አይደለም” ያሉት የካኤል ኤም የኢትዮጵያና የሱዳን ወኪል ሚ/ር ዲክ ቫን ኒወንሀውዘን፣ ወደ ኢትዮጵያ የሚያደርጉትን በረራ ሸሪክ በሆነው በኬንያ አየር መንገድ በኩል እንደሚያስተናግዱ ገልጸዋል።


 ካ ኤል ኤምን ጨምሮ አራት አየር መንገዶች ወደ ኢትዮጵያ የሚያደርጉትን በረራ ሰርዘዋል።


ካኤል ኤም በ90 አገራት በረራ የሚያካሂድ ሲሆን በአለም ላይ ካሉት አየር መንገዶች ቀደምት ነው።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar