fredag 14. mars 2014

ህዝቡ ለመለስ ፋውንዴሽን ገንዘብ እንዲያዋጣ እየተገደደ ነው

የኢህአዴግ ካድሬዎች በተለይ በአዲስ አበባና በአጎራባች ከተሞች ባሉ ቤቶች እየዞሩ ለመለስ ፋውንዴሽን ማቋቋሚያ ከ50 ብር ጀምሮ እንዲከፍሉ እያስገደዱ ነው። እድሮች በነፍስ ወከፍ ከ8 ሺ ብር ጀምሮ እንዲከፍሉ መመሪያ ተላልፎላቸዋል።
በዚህ መመሪያ የተሰላቹና የተበሳጩ ሰዎች “ወዴት እንሂድ” ሲሉ ለኢሳት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። የመለስ ፋውንዴሽን በወ/ሮ አዜብ መስፍን ሊቀመንበርነት የሚመራ ሲሆን የአቶ መለስን አስከሬን በቋሚነት የሚያርፍበትን ቦታ የማዘጋጀትና ስራዎቻቸውን ለህዝብ የማቅረብ አላማ አለው።
ምንም እንኳ መንግስት ለፋውንዴሽኑ ማሰሪያና ስራ ማስኬጃ በየአመቱ ገንዘብ የሚሰጥ ቢሆንም፣ ይህ ሳያንስ እያንዳንዱ ህዝብ ገንዘብ እንዲያወጣ መገደዱ አግባብ አለመሆኑን አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ። ገንዘብ መስጠትም ካለባቸው የኢህአዴግ ደጋፊዎች እንጅ ኢህአዴግን የማይደግፉት እንዲሰጡ መገደድ የለባቸውም ሲሉ እነዚህ አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ።
በእድሮች ላይ ሳይቀር የተጣለው የመዋጮ ግዴታ በበርካታ የእድር አባላት ላይ ቀርታ ፈጥሯል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar