onsdag 26. mars 2014

የሕገ መንግስቱ መሰረት የሆነው ቻርተር በኤርትራዊዉ በረከተ ሃብተ ስላሴ በሚመራ ኮሚሽን እንደዘጋጀ ተገለጸ


ኢሕአዴግ አዲስ አበባ ሲገባ፣ በጎሳ የተደራጁ ድርጅቶችን በማሰባሰብ ፣ በ1991 በተደረገው የአዲስ አበባ ኮንፈራንስ ፣ የሽግግር መንግስት ቻርተር ተብሎ የሚታወቀዉን ሰነድ እንዲጸድቅ ማስደረጉ ይታወቃል።
ቻርተሩ አሁን ያለውን በጎሳ ላይ የተመሰረተ ዘረኛ ፌዴራል አወቃቀር ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲገበር ያደረገ ከመሆኑም በተጨማሪ፣ በየትኛው አገር የሌለ፣ ጸረ-ኢትዮጵያዊ የብሄረሰቦች የመገንጠልን መብትን በሕግ ለመጀመሪያ ጊዜ የደነገገም እንደሆነ ይታወቃል።
ዶር ነጋሶ ጊዳዳ አባል የነበሩበት የሕገ መንግስት አርቃቂ ኮሚሽን፣ በቻርተሩ የተቀመጠዉን ፌዴራል አወቃቀርና የመገንጠል መብትን እንዳለ ሕገ መንስግቱ ዉስጥ እንዲካተት በማድረግ ፣ ቻርተሩ «ሕገ መንግስት» የሚል ሽፋን ተሰጥቶት፣ ኢዴሞክራሲያዊና ኢፍትሃዊ በሆነ መንገድ የአገሪቷ ሕግ እንዲሆን መደረጉም የሚረሳ አይደለም።
በኋላ እንደ ሕግ መንግስት የተወሰደው ይሄ ቻርተር፣ በአዲስ አበባ ኮንፍራንስ በኢትዮጵያዉያኖች እንደጸደቀ ቢነገርም፣ በተሰነይ/ ኤርትራ ፣ በአቶ ኢሳያስ አፈወርቂ፣ አቶ መለስ ዜናዊና አቶ ሌንጮ ለታ በተቋቋመው እና ኤርትራዊዉ ዶር በረከት ሃብተስላሴ በሚመሩት ግብረ ኃይል አስቀድሞ የተዘጋጀ እንደሆነ፣ የቀድሞ የኢትዮጵያ ፕሬዘዳንት የነበሩት ዶር ነጋሶ ጊዳዳ ይናገራሉ።
ዶር ነጋሶ በቅርቡ ዘሃበሻ ላይ ለአንባቢያን ባቀረቡት ጽሁፍ ፣ «There is also evidence that a task force including Bereket Habte Sellasie was established by Isayas, Meles and Lencho to draft the Charter and agreed upon between Meles and Lencho at Tesenai/Eritrea.” ሲሉ ነበር የነበረዉን ሁኔታ ለማስረዳት የሞከሩት።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar