onsdag 30. oktober 2013

የኢትዮምህዳር ጋዜጠኞች አደጋና ውሳኔ

አደጋው ከደረሰባቸው ጋዜጠኛ አንዱ ጌታቸው ወርቁ እንዳስታወቀዉ ለአደጋ የተጋለጡት የተሳፈሩበት ባጃጅ በሞተር ብስኪሌት በመገጨቱ ነዉ።የሃዋሳ ፍርድ ቤት ጉዳዩን ለማየት ሥልጣን የለውም መከሰስ ያለበትም ዋና አዘጋጁ ነው ሲሉ ጋዜጠኞቹ ያቀረቡትን ጥያቄ ዛሬ ከሰዓት ውድቅ አድርጓል።
ሶስት የኢትዮ ምህዳር ጋዜጠኞች ዛሬ በሃዋሳ ከተማ በደረሰባቸው የግጭት አደጋ መጎዳታቸዉን አስታወቁ ። ጋዜጠኖቹ አደጋው የደረሰባቸው ስለ ሃዋሳ ዩኒቨርስቲ ባወጡት ዘገባ ለቀረበባቸው ክስ የሲዳማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሰጣቸው ቀጠሮ መሰረት ሃዋሳ በተገኙበት ወቅት ነበር።አደጋው ከደረሰባቸው ጋዜጠኛ አንዱ ጌታቸው ወርቁ እንዳስታወቀዉ ለአደጋ የተጋለጡት የተሳፈሩበት ባጃጅ በሞተር ብስኪሌት በመገጨቱ ነዉ።የሃዋሳ ፍርድ ቤት ጉዳዩን ለማየት ሥልጣን የለውም መከሰስ ያለበትም ዋና አዘጋጁ ነው ሲሉ ጋዜጠኞቹ ያቀረቡትን ጥያቄ ዛሬ ከሰዓት ውድቅ ማድረጉን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ከአዲስ አበባ ዘግቧል ።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar